Saturday, December 20, 2014

ምስጋና

ወንድሜ ሆይ ለማመስገን የግድ ከክፍልህ አንደኛ መውጣት አያስፈልግህም። ዓመቱን ሙሉ ተመላልሰህ በሰላም ለመማር መብቃትህ ራሱ ከበቂ በላይ ምክንያት ነው። ለማመስገን ሮጠህ በአንደኝነት መሸለም አያሻህም። ዝለህ ሳትወድቅ ውድድሩን መጨረስህ ወይም በተመልካችነት መታደምህ ራሱ የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ዕድል ነው። 
ለማመስገን ምርጥና ዘመናዊ መኪና እስክትነዳ መጠበቅ ሞኝ ያስብልሃል። በማይሌጅ የበለጠገችው ኩርኩር መኪናህ ቀለበት መንገድ ላይ ሳትገትርህ ጎታች መኪና ጥበቃ ብርድና ሐሩር ላይ ሳታቆምህ በደህና ቤትህ መግባትህ የሎተሪ ያህል አስደሳች ዕጣ ነው።

ለማመስገን ከተጠናወተህ ደዌ እስክትፈወስ መጠበቅ አይተው ከሚያምኑት ተጠራጣሪዎች ጎራ ያቆምሃል። ግን ቆመህ መሄድህ ራሱ ተአምር እንደሆነ አምነህ ብታመሰግን ያምርብሃል።

No comments:

Post a Comment