ተደርቦና ተደራርቦ
ማዕበል የተለመደ የውኃ ላይ ነውጥ ቢሆንም አደገኛ የሚሆነው በተደራራቢነቱ ነው። እያንዳንድዋ የውሃ ጉማጅ ትጋፋለች። በአንዱ ተንገዳግዶ መቆም ሲቻል አንዱ ባንዱ ላይ እየተነባበረ ሲመጣ ግን ከአቅም በላይ ይሆናል። እንዲሁም ችግር የሕይወት ጥላ ቢሆንም የበለጠ አስቸጋሪ የሚሆነው ተደርቦና ተደራርቦ ሲመጣ ነው። ሁለቱን አስማሚ ፍች ከሠጠናቸው በኋላ ጥቂት ማብራሪያ ማከል ይኖርብናል። ተደርቦ ስንል ከዚያ ቀደም ብሎ የተከሰተው ችግር ከመፈታቱ በፊት ሌላው የመድረሱን እውነታ ተከትለን ነው። ተደራርቦ ካልን ደግሞ ከመደረብም አልፎ በላይ በላዩ ተቆልሏል ማለት ነው። በአገራችን መደረብ ወይም መደራረብን ጥሩ አድርገው የሚገልጡ አባባሎች አሉን። የመጀመሪያው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ የሚለው ነው። በቡሃ ላይ ቆረቆር ሊባልም ይችላል። በድንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ ወይም ከአባ ቁፍር እሸት ተበልቶለት እሚሉትም ቢሆኑ ጥሩ ምሳሌዎች ናቸው።
No comments:
Post a Comment